languageIcon
search
search
brightness_1 ወደመጸዳጃ ቤት ሲገቡና ሲወጡ በሐዲሥ የተዘገቡ ዚክሮችን ማለት፡፡

ወደመጸዳጃ ቤት የሚገባ ሰው በትክክለኛ የሒዲሥ ዘገባዎች የሠፈሩት ቃላት ማለቱ ነቢያዊ ፈለግ ነው፡፡ 

ከአነስ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- እንደተወራው፣ ‹‹የአላህ መልእክተኛ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን- ወደመጸዳጃ ቤት ሲገቡ፣ “አልላሁምመ ኢንኒ አዑዙ ቢከ ሚነልኹቡሢ ወልኸባኢሢ፡፡ /አላህ ሆይ! እርኩስ ከሆኑ ወንድ፣ እርኩስ ከሆኑ እንስት ሸይጣኖች ባንተ እጠበቃለሁ፡፡/” ይሉ ነበር፡፡›› ብለዋል፡፡ ሐዲሡን ቡኻሪ በሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (6322)፣ ሙስሊም ደግሞ በቁጥር (375) ላይ ዘግበውታል፡፡

‹‹ኹቡሥ›› ማለት ወንድ ሸይጣኖች ማለት ሲሆን ‹‹ኸባኢሥ›› ደግሞ እንስት (ሴት) ሸይጣኖች ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ጥበቃ የሚያስፈልገው ከወንድ ሸይጣኖችና ከሴት (እንስት) ሸይጣኖችም ነው፡፡

ቃሉ ‹‹ኹብሥ›› ተብሎ  ከተነበበ ትርጉሙ እርኩስና መጥፎ ከሆኑ መናፍስት እንዲሁም ከተንኮልና ከተንኮለኞች ጥበቃን መጠየቅ ማለት ይሆናል፡፡ ስለዚህ በዚህ መልኩ ማለቱ ሁሉንም የሚያጠቃል በመሆኑ ተመራጭ ነው፡፡

- ከመጸዳጃ ቤት የሚወጣ ሰው ሲወጣ የሚከተለውን ማለቱ ነቢያዊ ፈለግ ነው፡-

ሙስነድ በተሰኘው የአሕመድ የሐዲሥ መድብል ላይ እንዲሁም በአቢ ዳዉድና አት-ቲርሚዚይ የሐዲሥ ዘገባ ላይ እንደሰፈረውና አል-አልባኒይ ትክክለኛቱን ባረጋገጡት የዓኢሻህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- ሐዲሥ ዓኢሻ፣ ‹‹የአላህ መልእክተኛ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን- ከመጸዳጃ ቤት ሲወጡ፣ “ጉፍራነክ፡፡ /ጌታዬ ሆይ! ምሕረትህን ለግሰኝ፡፡/” ይሉ ነበር፡፡ አሕመድ ሐዲሡን በሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (25220)፣ አቡ ዳዉድ በቁጥር (30) እንዲሁም አት-ቲርሚዚ በቁጥር (7) የዘገቡት ሲሆን አል-አልባኒይ የሐዲሡን ትክክለኛነት አረጋግጠዋል፡፡ ተሕቂይቁ ሚሽካቱ-ል-መሳቢይሕ ቅጽ ፡ 1 ገጽ፡ 116፡፡

brightness_1 ኑዛዜን መጻፍ ነቢያዊ ፈለግ ነው

ማንኛውም ሙስሊም በሕመም ላይ ሳለም ሆነ በጤንነት ላይ እያለ ኑዛዜውን መጸፉ ነቢያዊ ፈለግ ነው፡፡ የአላህ መልእክተኛ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “ማንኛውምኑዛዜ ሊያደርገው የሚፈልገው አንዳች ነገር ኖሮት በእሱ ዘንድ ኑዛዜው ተጽፎ ካልሆነ በስተቀር ሁለት ሌሊቶችን ማሳደር የሙስሊም መብት አይደለም፡፡” ብለዋል፡፡ ቡኻሪ በሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (2783)፣ ሙስሊም በቁጥር (1626) ላይ ከኢብን ዑመር -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- ዘግበውታል፡፡ በዚህ ሐዲሥ ውስጥ ሁለት ሌሊቶችን መጥቀሳቸው ጊዜውን ለመገደብ ሳይሆን፣ የተፈለገው ሃሳብ ኑዛዜው ሳይጻፍ ጥቂት ቀናት እንዳያልፉት ነው፡፡ ምክንያቱም ይህ ሰው መቼ ይሙት ስለማይታወቅ ነው፡፡ ይህ ሁሉም ሊተገብረው የሚገባ ነቢያዊ ፈለግ ነው፡፡ 

እንደዘካት፣ ሐጅና ማካካሻ ዓይነት  በእሱ ላይ ያሉ የአላህ ሐቆችን ወይም እንደእዳና አደራን መመለስ ዓይነት በእሱላ ላይ ያሉ የሰው ልጅ ሐቆች ካሉ እንዲፈጸምለት ኑዛዜ መተው ነቢያዊ ፈለግ ሳይሆን ግዴታ ነው፡፡ ምክንያቱም ይህ ሁኔታ ግዴታ የሆኑ ሐቆችን ከመወጣት ጋር የተያያዘ በመሆኑ ነው፡፡ ዋና መሰረታዊ መመሪያ ቃሉ ደግሞ [ግዴታ የሆነ ተግባር ከእሱ በስተቀር  የማይሟላ ከሆነ ይህ ሁኔታ በራሱ ግዴታ ነው፡፡] የሚለው ነው፡፡

brightness_1 ሰላትን መጠባበቅ

ሰላትን መጠባበቅ በቀን ውስጥ ታላላቅ ምንዳዎች ከሚመዘገብባቸው ነቢያዊ ፈለግ ከሆኑ ተግባራት መካከል አንዱ ነው፡፡

ለዚህም ማስረጃው፡-

አቢ ሁረይራህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ -የአላህ እዝንትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “አንዳቸሁ ሰላት እስካሰረችው ድረስና ከሰላት በስተቀር ወደቤተሰቡ እንዳይመለስ ሌላ ነገር ከሌለ ሰላት ውስጥ ነው፡፡” ብለዋል፡፡ ሐዲሡን ቡኻሪ ሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (659)፣ ሙስሊም ደግሞ በቁጥር (649) ዘግበውታል፡፡ ይህ ሰው ሰላትን በመጠባበቁ ምክንያት የሰላትን ምንዳ ያገኛል፡፡

አቢ ሁረይራህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- እንዳስተላለፉት የአላህ  መልእክተኛ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “አንዳቸሁ ዉዱእ እስካላበላሽና በመስገጃው ላይ እስካለ ድረስ መላእክቶች፣ ‹አላህ ሆይ! ወንጀሉን ማርለት፡፡ አላህ  ሆይ! እዘንለት፡፡›በማለት ዱዓ ያደርጉላታል፡፡ አንዳቸሁ ሰላት እስካሰረችው ድረስና ከሰላት በስተቀር ወደቤተሰቡ እንዳይመለስ ሌላ ነገር ከሌለ ሰላት ውስጥ ነው፡፡” ብለዋል፡፡ ሐዲሡን ቡኻሪ ሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (659)፣ ሙስሊም ደግሞ በቁጥር (649) ላይ ዘግበውታል፡፡ በሙስሊም  ሌላ ዘገባ፣ “በዚያ ላይ እስካልተጎዳ፣ በዚያ ላይም ወዱእ እስካለበላሸ ድረስ፡፡” ብለዋል፡፡ ሐዲሡን ሙስሊም በሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (649) ላይ ዘግበውታል፡፡

ይህ ማለት ምንዳው በተቀመጠበት ሥፍራ ላይ እንዳች ጎጂ ነገር አለማጋጠምና ወዱእ ለአመፍታት (አለመበላሸት) በሚሉት መሥፈርቶች የተሳሰረ ነው፡፡

 

brightness_1 መፋቂያ

መፋቂያ በጊዜ ካልተገደበና በማንኛውም ጊዜ ሊተገበሩ ከሚችሉ ነቢያዊ ፈለጎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ነቢዩ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “በመፋቂያ ላይ አበዛሁባችሁ፡፡” እስከሚሉ ድረስ በእሱ ላይ በብዛት ያነሳሱ ነበር፡፡ ሐዲሡን ቡኻሪ በሐዲሥ ቁጥር (888) ከአነስ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- ዘግበውታል፡፡ ነቢዩ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን- “መፋቂያ ለአፍ ንጽሕናን  መጠበቂያ ለጌታ ማስደሰቻ ነው፡፡” ብለዋል፡፡ ሐዲሡን አን-ነሳኢይ በሐዲሥ ዘገባ ቁጥር (5) ከዓኢሻህ -አላህ መልካም ሥራዎቻችሁን ይውደድላቸው- የዘገቡት ሲሆን አል-አልባኒይም የሐዲሡን ትክክለኛነት አረጋግጠዋል፡፡ አል-ኢርዋእ ቅጽ ፡ 1 ገጽ ፡ 105፡፡   

የመፋቂያ ነቢያዊ ፈለግነት የሚበረታው ከዚህ በላይ በሳለፍናቸውና ሌሊት እንደመነሳት፣ ዉዱእ በሚደረግበት ወቅት፣ በእያንዳንዱ ሰላት ወቅትና ወደቤት በሚገባበት ወቅት በመሳሰሉት በቀንና በምሽት በሚደጋገሙ ሥፍራዎች ላይ ነው፡፡ -አላህ ይበልጥ ዐዋቂ ነው-፡፡

brightness_1 ለእያንዳንዱ ሰላት ዉዱእን ማደስ

አንድ ሙስሊም ከእያንዳንዱ ሰላት ዉዱእ ማድረጉ ነቢያ ፈለጎችን እንደመከተል ይቆጠርለታል፡፡ ለምሳሌ ለመግሪብ ሰላት ዉዱእ ካደረገና በዚሁ ወዱእ የመግሪብ ሰላት ከሰገደ በኋላ ዉዱእ ያለው ቢሆንም የዒሻእ ሰላት ከደረሰ ዉዱእ ማድረጉ ነቢያዊ ፈለግን እንደመተግበር ይታሰብለታል፡፡ ነቢያዊ ፈለጉ ለእያንዳንዱ ሰላት አዲስ ዉዱእ ማድረጉ ነው፡፡

ለዚህ  ማስረጃው፡-

ቡኻሪ እንደዘጉት፣ ‹‹ነቢዩ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን- በእያንዳንዱ ሰላት ዉዱእ ያደርጉ ነበር፡፡›› ብለዋል፡፡ ሐዲሡን ቡኻሪ በቁጥር (214) ዘግበውታል፡፡

እንደዚሁም ማንኛውም ሙስሊም ቀኑን ሙሉ ንጹሕ መሆኑ ከነቢያዊ ፈለጎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ሠውባን -አላህ መልካም ሥራዎቻቸው ይውደድላቸው- እንዳስተላለፉት ነቢዩ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “ሙእሚን ካልሆነ በስተቀር ንጽሕናን አይጠብቅም፡፡” ብለዋል፡፡ ሐዲሡን አሕመድ በቁጥር (22434)፣ ኢብን ማጀህ በቁጥር (277)፣ አድ-ዳረሚይ በቁጥር 655) የዘገቡት ሲሆን አል-አልባኒይ ትክክለኛነቱን አረጋግጠዋል፡፡ ሰሒሑ-ልጃሚዕ ቅጽ ፡ 1 ገጽ ፡ 225፡፡