languageIcon
search
search
brightness_1 ሰላምታ ማቅረብ ከነቢያዊ ፈለጎች ነው፡፡

ማስረጃዎቹ በጣም በርካታ ናቸው፡፡ ከእነር መካከል፡- አቢ ሁረይራህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “አንድ ሙስሊም በሙስሊም ላይ ያለው መብት ስድስት ነው፡፡” አሉ፡፡ ‹የአላህ መልእክተኛ ሆይ! እነርሱ ምን ምን ናቸው? ተባሉ፡፡ እሳቸውም፣ “ስታገኘው ሰላም በለው፡፡ ከጠራህ ምላ ስጠው፡፡ ምክር ከጠየቀህ ምክር ለግሰው፡፡ አነጥሶ አላህን ካመሰገነ አላህ ይማርህ በለው፡፡ ከታመመ ጎብኘው፡፡ ከሞተ ተከተለው፡፡” አሉ፡፡ ሙስሊም በቁጥር (2162) ላይ ዘግበውታል፡፡

- ሰላምታን መመለስ (ምላሽ መስጠት) ግዴታ ነው፡፡ ለዚህም ማሰረጃው፡-

አላህ እንዲህ ብሏል፣ “በሰላምታም በተከበራችሁም ጊዜ ከርሷ ይበልጥ ባማረ (ሰላምታ) አክብሩ ወይም (እርሷኑ) መልሷት አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ተቆጣጣሪ ነውና፡፡” (አን-ነሳእ ፡ 86)፡፡

ግዴታ የመሆኑ መነሻ የሚከለክለው አንዳች ከልካይ ካልከለከለው ነው፡፡ ከዑለሞች መካከል አንዱ ብቻ ካልሆኑ በስተቀር ይህን ሃሳብ በጋራ ሃሳብነት  ሁሉም አስተላልፈውታል፡፡ ከእነዚህ ዑለሞች መካከል፡- ኢብን ሐዝም፣ ኢብን ዐብዱ-ልበር ፣ ሸይኽ ተቂይዩ-ድዲንና ሌሎችም ይገኛሉ፡፡ አዳቡ-ሽሸርዒየህ ቅጽ፡ 1 ገጽ ፡ 356፡፡ የአር-ሪሳለህ ድርጅት እትም፡፡

- በላጩ የሰላምታና የምላሸ ቃል እንዲሁም መሉ የሆነው የሰላምታ ቃል፡- “አስሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱ-ልላሂ ወበረካቱሁ፡፡” ነው፡፡ ይህ መልካሙና ሙሉው ሰላምታና፡፡ 

ኢብን አል-ቀይዪም -አላህ ይዘንላቸው- እንዲህ ብለዋል፣ ‹‹  -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን- አስተምህሯቸው ሰላምታን ‹‹ወበረካቱሁ›› እስከሚለው ድረስ ማጠናቀቅ ነው፡፡›› ዛዱ-ልሚዓድ ቅጽ ፡ 2 ገጽ ፡ 417፡፡

ሰላምታን ማሰራጨት፡- ነቢያዊ ፈለግ ሲሆን ትልቅ ትሩፋት ስላለውም ይበረታታል፡፡ አቢ ሁረይራህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “ነፍሴ በእጁ በሆነችው እምላለሁ! እስክታምኑ ድረስ ጀነት  አትገቡም፡፡ እስከምትዋደዱ ድረስ አታምኑም፡፡ ከፈጸማችሁት የምትዋደዱበትን አንዳች ነገር ላመላክታችሁን? በመካከላችሁ ሰላምታን አሰራጩ፡፡

brightness_1 ችግር እስካስገደደ ድረስ ሰላምታን ሶስት ጊዜ መደጋገም፡፡

ለመጀመሪያ ጊዜ ሰላምታ ሲያቀርብለት ሙስሊም የሆነው ሰው መስማቱን ከተጠራጠረ ሁለት ጊዜ መደጋገሙ የተወደደ ነው፡፡ ካልሰማም ሶሰት ጊዜ፡፡ ብዙ ሰዎች የተሰበሰቡበት ቦታ ሲገባም እንዲሁ ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ትልቅ ስብሰባ መካከል ሲገባ ሰዎቹ በርካታ ከሆኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰላምታ ሲያቀርብ በመጀመሪያው ረድፍ ካሉት በስተቀር ሌሎች አይሰሙትም፡፡  ስለዚህ በስብሰባው ውስጥ ያሉትን ሁሉ ለማጠቃለል ሶስት ጊዜ መደጋገም   ያስፈልጋል፡፡

ለዚህ ማሰረጃው፡- አነስ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- ‹‹ነቢዩ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን- አንዳች ቃል ከተናገሩ ሰዎችን ከእሳቸው እስኪረዷቸው ድረስ ሶስት ጊዜ ይደጋግሙት ነበር፡፡ ወደሰዎች ስብስብ ሲመጡ ሰላም ይሏቸዋል፡፡ ሶሰት ጊዜም ሰላም ይሏቸዋል፡፡›› ብለዋል፡፡ ቡኻሪ በቁጥር (95) ላይ ዘግበውታል፡፡

ከአነስ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- ሐዲሥ ችግር እስካስገደደ ድረስ አንድ ቃል መረዳትን እስከያገኝ ድረስ ሶሰት ጊዜ እንደሚደጋገመው ሰላምታን ሶስት ጊዜ የመደጋገምን ነቢያዊ ፈለግነት ጭብጥ መውሰድ እንችላለን፡፡

 

brightness_1 ወደቤት ሲገቡ ሰላምታ ማቅረብ ነቢያዊ ፈለግ ነው፡፡

ይህ ተግባር በሁሉም የሰላምታ ዓይነቶች ላይ ይካተታል፡፡ ይህም  ግለሰቡ ጥርሱን ከፋቀ በኋላ ነው፡፡ ምክንያቱም ወደቤት ሲገቡ ጥርሰን መፋቅ (መፋቂያ መጠቀም) ነቢያዊ ፈለግ ነው፡፡ ይህ መፋቂያ ነቢያዊ ፈለግ መሆኑንን የሚያረጋጠው አራተኛው ስፍራ ነው፡፡ ሙስሊም በዘገቡት ሐዲሥ ላይ ዓኢሻህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው-፣ ‹‹ ነቢዩ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን- ቤታቸው ሲገቡ ጥርሳቸውን መፋቅ ይጀምራሉ፡፡›› ብለዋል፡፡ ሙስሊም በቁጥር (253) ላይ ዘግበውታል፡፡ ነቢዩ    -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን- ቤታቸው ሲገቡ ጥርሳቸውን በመፋቅ ይጀምሩ ነበር፡፡ ከዚያ ለቤተሰቦቻቸው ሰላምታ ያቀርቡ ነበር፡፡ የተወሰኑ ዑለሞች፣ ‹‹ወደቤት ስትገባ ሰላምታ ማቅረብህና የትኛውም ቤት አንድም ሰው ባይኖርም ሰላምታ ማቅረብህ ነቢያዊ ፈለግ ነው፡፡›› ብለዋል፡፡ ይህም አላህ እንዲህ በማለቱ ነው፣ “ቤቶችንም በገባችሁ ጊዜ ከአላህ ዘንድ የኾነችን የተባረከች መልካም ሰላምታ በነፍሶቻችሁ ላይ ሰላም በሉ፤ እንደዚህ አላህ አንቀጾችን ለናንተ ያብራራል፤ ልታውቁ ይከጅላልና፡፡” (አን-ኑር ፡ 60)፡፡

ኢብን ሐጀር -አላህ ይዘንላቸው-፣ ‹‹በራስ ላይ ሰላምታን ማቅረብ ሰላምታን በማሰራጨት ሥር ይጠቃለላል፡፡ ይህም አንድም ሰው በሌለበት ሥፍራ የገባም ቢሆን ማለት ነው፡፡ ይህም አላህ እጅግ የላቀው ጌታ፣ “ቤቶችንም በገባችሁ ጊዜ ከአላህ ዘንድ የኾነችን የተባረከች መልካም ሰላምታ በነፍሶቻችሁ ላይ ሰላም በሉ፤” (አን-ኑር ፡ 60) ስላለ ነው፡፡›› ብለዋል፡፡ አል-ፈትሕ ሰላምታን በማሰራጨት ምዕራፍ ሥር ሐዲሥ ቁጥር (6235)ን ይመልከቱ፡፡

  1. ፋይዳ፡- ከዚህ በላይ ከሰፈረው ወደቤት ሲገባ ሶስት ተግባራትን መፈጸም ነቢያዊ ተግባር ነው፡፡ እነርሱም፡-

የመጀመሪያው፡- ሌሊት ቢሆንም -እጅግ የላቀውን- አላህን ስም ማውሳት

ጃቢር ኢብን ዐብዲላህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውነ ይውደድላቸው- የአላህ መልእክተኛ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ ይውደድላቸው- ነቢዩ -የአላህ እዝነትና ሰላምታ በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “አንድ ሰው ወደቤቱ ሲገባ በምግባቱና በምግቡ ላይ የአላህን ስም ካወሳ ሸይጣን፡- ማደሪያና እራት የላችሁም ይላል፡፡ ሰውዬው ሲገባ በመግባቱ ላይ የአላህን ስም ካላወሳ ሸይጣን፡- ማደሪያ አገኛችሁ፡፡ በምግቡ ላይ የአላህን ስም ካላወሳ ሸይጣን፡- ማደሪያና እራት አገኛችሁ፡፡ ይላል፡፡” ሲሉ መስማታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ሐዲሡን ሙስሊም በሐዲሥ ቁጥር (2018) ላይ ዘግበውታል፡፡

ሁለተኛው፡- ከዚህ በላይ በዓኢሻህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- ባወሩት ሐዲሥ መሰረት ጥርስን መፋቅ    (መፋቂያ መጠቀም)፡፡

ሶስተኛው፡- ለቤተሰቡ ሰላምታ ማቅረብ፡፡

brightness_1 መልካም ንግግር ሰደቃህ (ምጽዋት) በመሆኑ መተግበሩ ነቢያዊ ፈለግ ነው፡፡

በመገኛኘት ወቅትም ሆነ አብረው በሚቀመጡበት ወቅት ወይም በማንኛውም አጋጣሚ መልካም ንግግር ነቢያዊ ፈለግ ነው፡፡ ምክንያቱም ሰደቃህ (ምጽዋት) ነውና፡፡

ለዚህ ማስረጃው፡- አቢ ሁረይራህ -አላህ መልካም ሥራዎቻቸውን ይውደድላቸው- እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ -የአላህ እዝነትና ሰላም በእሳቸው ላይ ይሁን-፣ “መልካም ንግግር ሰደቃህ (ምጽዋት) ነው፡፡” ብለዋል፡፡ ቡኻሪ በቁጥር (2989)፣ ሙስሊም በቁጥር (1009) ላይ ዘግበውታል፡፡

በበርካታ ሰዎች አንደበት ላይ አብዛኛውን ጊዜ መልካም ንግግር አይጠፋም፡፡ ይሁን እንጂ ምንዳን ቢያስቡ ኖሮ በርካታ ምንዳዎችን ከመጎጸፋቸው ባሸገር እጅግ በርካታ ምጽዋትን (ሰደቃዎችን) ባካበቱ ነበር፡፡

ሸይኻችን ኢብን ዑሠይሚን -አላህ ይዘንላቸው-፣ ‹‹መልካም ንግግር ማለት ለአንድ ሰው፣ ‹እንዴት ነህ? ጤናህ እንዴት ነው? ወንድሞችህ እንዴት ናቸው?

ቤተሰቦችችህ እንዴት ናቸው? እና ወ.ዘ.ተ ማለትህ ነው፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ቃላት ወዳጅህ ደስታን ያሰርጻሉ፡፡ እያንዳንዱ መልካም ቃል አላህ ዘንድ ምጽዋትህ (ሰደቃህ)፣ ምንዳህና ሽልማትህ ነው፡፡›› ብለዋል፡፡ ሸርሑ ሪያዱ-ስሳሊሒን ቅጽ ፡ 2 ገጽ ፡ 996 በመገናኘት ወቅት መልካም ንግግርና መልካም ገጽታ የተወደደ ሰእለመሆኑ ምዕራፍ፡፡